[ad_1]
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ትግራይ ክልል ውስጥ ላለው ጦርነት ላለፉት 20 ዓመታት የትግራይ ሕዝብ ነፃነት ግንባርን ሲደግፉ የቆየ ያሉትን የአሜሪካ መንግስት አስተዳደር ተጠያቂ ማድረጉን APን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ አስነብቧል።
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ለሚካሄደው ጦርነት ኤርትራን ተጠያቂ ማድረጉም መሠረተ ቢስ ነው ሲሉ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኡስማን ሳሌህ መግለጫ ሰጥተዋል።
ኡስማን ሳሌህ ትናንት ሰኞ ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በፃፉት እና በምክር ቤቱ በተሰራጨዉ ደብዳቤ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በክልሉ ጣልቃ በመግባት እና በማስፈራራት «ተጨማሪ ግጭትን እና አለመረጋጋትን ያስከትላል» ሲሉ ከሰዋል።
የአሜሪካው አሶሽየትድ ፕሬስ «በግምት ስድስት ሚሊዮን ሕዝብ ይኖርበት ከነበረዉ የትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት አንድ ሦስተኛውን አካባቢዉን ለቅቆ ሸሽቶአል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ በጦርነቱ እንደተገደሉም ይገመታል። በአሁኑ ወቅት የመንግሥት ወታደሮች ለበርካታ ግፎች ተጠያቂ ናቸው ከሚባሉት ከጎረቤት ኤርትራ ወታደሮች ጋር በትብብር ላይ ናቸዉ» ሲል ስለመፃፉ ዶቸ ቨለ አስነብቧል።
Related
[ad_2]
Source link
GIPHY App Key not set. Please check settings